Mission of the city administration

  • በከተማ አስተዳደራችን ያሉትን የመልካም አስተዳደር ችግሮች በመለየት ህብረተሰባችንን በማሳተፍ   የመሰረተ ልማት አዉታሮችን በመዘርጋት መላዉ የከተማችን ህዝብ በኢኮኖዊያዊና በማህበራዊ ዘርፎች ተጠቃሚ በማድረግ ሰላም ፤ዴሞክራሲ፤እኩልነትና ፍትሃዊነትን በማስፈን ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት መስራት ነዉIdentifying the problems of good governance in our city administration, involving our society, developing infrastructure networks, benefiting the entire people of our city in the economic and social sectors, establishing peace, democracy, equality and justice, and working to provide fast and efficient services.

 

 

Vision

  • በከተማ  አስተዳደራችን ደረጃ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ተፈተዉ ፤የመሰረተ ልማት አዉታሮችና ኢንቨስትመንት ተስፋፍተዉ ዲሞክራሲ፤ ሰላም ፤እኩልነትና ፍትሃዊነትን በማረጋገጥ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት ህዝባችን የልማቱ ተጠቃሚ ሆኖ ማየት At the level of our city administration, the problems of good governance have been solved; infrastructure networks and investment have expanded, democracy; Peace, ensuring equality and justice by providing fast and efficient service and seeing our people benefit from the development.

 

 

History of the city with summary

የከተማዋ ገጽታ

የደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር ሥር የምትገኝ ክልሉ በመካከለኛ ደረጃ ከፈረጃቸው ከተሞች መካከል አንዷ ነች፡፡ ከተማዋ የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር ርእሰ ከተማ ከኢትዮጵያ ርዕሰ ከተማ ከአዲስ አበባ 13ዐ ኬ.ሜ ርቀት የምትገኝና ከክልሉ ርእሰ ከተማ ባህር ዳር በ 695 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ትገኛለች፡፡ Debrebarhan city administration is under the administration of North Showa Zone of the Amhara National Regional Government and is one of the middle-class cities in the region. The city is the administrative capital of North Shewa Zone, which is 13 km away from Ethiopia's capital, Addis Ababa, and 695 km away from Bahr Dar, the capital of the region.

የደብረብርሃን ከተማ ታሪካዊ አመጣጥ

የደ/ብርሃን ከተማ በአፄ ዘርያእቆብ ዘመነ መንግስት በ1446 ዓ.ም የተቆረቆረች ጥንታዊ ከተማ ነች፡፡ የደብረበርሃን ከተማ ስያሜውን ያገኘችው ከሁለት ቃላት የተወሠዱ ትርጓሜዎች ነው እነሱም ደብረ/አጥቢያ ቦታ/ ማለት ነው፡፡ ብርሃን የሚለው ደግሞ በደስታ ተ/ወልድ የተዘጋጀው የአማራኛ መዝገበ ቃላት እንደሚገልፀው የአጼ ዘርያእቆብ የቅድሰት ስላሴ መቅደስ /ደብር/ የሠሩባት ብርሃን ስለወረደባት በመቅደሱ ስም ደብረብርሃን ተባለ ይላሉ፡፡ ብርሃኑ የታየበት ቀን መጋቢት 1ዐ/1446 ዓ.ም ቀን በቁርባን ጊዜና ሌሊት መዘምራን ሲያገለግሉ ታየ ተብሎ ይነገራል፡፡ ከዚህ በፊት ግን ደብረብረሃን ደብረ ኤባ ትባል እንደነበር በአንዳንድ ፀሐፊዎችና በአፈ ታሪክ ይነገራል፡፡The city of D/Barhan is an ancient city that was founded in 1446 AD during the reign of Emperor Zaryaekob. The city of Debreberhan got its name from the interpretations of two words, which mean "debre/local place". According to the Amharic Dictionary prepared by Joy T/Wold, the meaning of "light" is that it was called "Debre Berhan" after the light that they built on the Temple of the Holy Trinity. It is said that the light appeared on March 1st, 1446 A.D., when he was seen serving in the choir during the Eucharist and at night. But before that, Debrebrehan was called Debre Eba, according to some writers and legends.

        ምንጭ ፡- ታደሠ አይቸው ከአ/አበባ ዮኒቨርሲቲ የደ/ብርሃን ታሪካዊ እድገት ከተመሠረተበት እስከ 1966 አብዮት ፍንዳታ በአማርኛ ተተርጉሞ የቀረበ፡፡

የከተማዋ የቆዳ ስፋት

        ደ/ብርሃን ከተማ በ9 የከተማ ቀበሌዎችና በ5 የገጠር ንኡስ ቀበሌዎች የተከፋፈለች ሲሆን የቆዳ ስፋቷም 18081.95 ሄክታር የሚሽፍን የቆዳ ስፋት አላት፡፡ De/Barhan city is divided into 9 urban kebeles and 5 rural sub-kebeles and its surface area is 18081.95 hectares.

የከተማዋ መልከዓ ምድራዊ አቀማመጥ

       ከተማዋ በ90 4ዐ ሰሜን ኬክሮስ /Latitude/ እና በ39 3ዐ ምስራቅ ኬንትሮስ /longitude/ ላይ ትገኛለች፡፡ ከባህር ወለል በላይ በአማካይ 275ዐ ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኝ ስትሆን የመሬት አቀማመጧም ሜዳ 86% ወጣ ገባ 1ዐ% ተራራማ 4% ሲሆን የአፈር ዓይነቷም መረሬ፣ ቀይና ቡናማ ነው፡፡

 

 

የከተማዋ የአየር ንብረት ሁኔታ

      የደብረብርሃን ከተማ ሙሉ ለሙሉ የአየር ንብረቷ ደጋማ ሲሆን በአማካይ የሙቀት መጠን 1ዐ39 ሲ.ግ ከፍተኛው እስከ 24 ሲ.ግ ይደርሣል፡፡ የቅዝቃዜ መጠን በ2ዐዐ4 ዓ.ም ታህሣስና ጥር ወር ውስጥ

 ከዐ በታች -2ዐ    ደርሶ እንደነበር ማስታወስ ይቻላል፡፡ አማካይ የዝናብ መጠኗም 946 ሚ.ሜ ነው፡፡ 

የከተማዋ የህዝብ ብዛት

         የከተማዋ የሕዝብ ብዛት የበደብረ ብርሃን ከተማ ገንዘብና አካባቢ ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት የስነ ህዝብ መረጃ እንደሚያመለክተው በከተማ ወንድ 89,579   ሴት 98,934  በድምር 188,513 ህዝብ እንደሚኖር ያስረዳል፡፡           

  1.  በአራቱም አቅጣጫ ወረዳውን የሚያዋስኑ ፡-
  1. በሰሜን ባሶና ወራና ወረዳ ሣሪያ ቀበሌ
  2. በደቡብ ባሶና ወራና ወረዳ ኮር ማርገፊናያ ቀበሌ
  3. በምስራቅ ባሶና ወራና ወረዳ ውሻውሺኝ ቀበሌ
  4. በምእራብ ባሶና ወራና ወረዳ አንጐለላ ቀበሌ
  1. የከተማው ቆዳ ስፋት 18081.95 ሄክታር
  2. የከተማው የአየር ሁኔታ ፡-
    • ደጋ   ------------- 100%
    • ወይና ደጋ  ……. %
    • ቆላ ………………%
  3.  የከተማው መልክዓ ምድር
    • ተራራማ  4  %
    • ሸለቆማ  10  %
    • ሜዳማ   86 %

 

  1. በተማ አስተዳደሩ የሚገኙ ወንዞችና ኃይቆች

           በጋ ከክረምት የሚፈሱ ወንዞች ፡-

    • በሬሣ  ወንዝ ከተማዋን መሃል ለመሀል አቋርጦ የሚያልፍ

           በክረምት ብቻ የሚፈሱ ወንዞች ፡-

    • ዳለቻ ወንዝ
    • ሙዘይን ወንዝ

          በከተማ አስተዳደሩ  የሚገኙ ገባር ወንዞች

  • በሬሣ ወንዝ   ገባርነቱ  ለ ጀማ ወንዝ
  • ዳለቻ        ገባርነቱ   ለ በሬሣ ወንዝ
  • ሙዘይን      ገባርነቱ  ለ ዳለቻ ወንዝ 

       በከተማ አስተዳደሩ  የሚገኙ ኃይቆች ፡-

    • ሰው ሠራሽ ኃይቅ ፡-   አታክልት ንኡስ ቀበሌ ግድብ 
  • የተፈጥሮ ኃይቅ   የለም
  1. በከተማው የሚነገሩ ቋንቋዎች
  • አማርኛ
  • ኦሮምኛ
  • ጉራግኛ
  • ትግሪኛ
  1. በከተማው የሚገኙ ብሄረሰቦች
  • የአማራ ብሄረሰብ
  • የኦሮሞ ብሄረሰብ
  • የጉራጌ ብሄረሰብ
  • የአርጎባ ብሄረሰብ
  • የትግሬ ብሄረሰብ
  1. በከተማው የሚገኙ የኃይማኖት ተቋማት ብዛ
  1. ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አብያተ ክርስቲያን ብዛት  19
  2. መስኪድ ብዛት  2
  3. የካቶሊክ ቸርች ብዛት  1
  4. ኘሮቴስታንት ቸርች ብዛት 13
  1. በከተማ አስተዳደሩ ውስጥ የሚገኙ የቱሪስት መስህብ 
    • ስላሴ ቤተክርስቲያን 
    • ኃይለማርያም ማሞ ት/ቤት
    • ትክል ድንጋይ ቀበሌ 7
    • የሩፋኤል ፀበል ቀበሌ 4
    • የአፄ ዮሐንስ ቤተ መንግስት ፍርስራሽ ልቼ
    • ማለፊያ ምንጭ መምህራን ተቋም ፊት ለፊት
  2. የከተማ አስተዳደሩ  የደን ሽፋን   29.955 ሄ/ር
  3. በከተማ አስተዳደሩ  ለእርሻ የዋለ መሬት በሄ/ር 3485 ሄ/ር
  4. በከተማ አስተዳደሩ ለእርሻ ስራ ያልዋለና ወደ ፊት ሊውል የሚችል መሬት